Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 84 ቅዱስ አምላክ ሰውን ሊያድን የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ቅዱስ አምላክ ሰውን ሊያድን፥
ወደ ዓለም ላከ ልጁን።
አማኞቹ
ይሰግዳሉ ለርሱ።
ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ ነው
አምላክ ፀባኦት።
፪፡ አምላክ ሆይ፥ እናመስግንህ፤
በምድር ይስፋ ግዛትህ።
የአንተ ቃል
ሕይወትን ይሰጣል።
ቅዱስ . . .።
፫፡ ቤተ ክርስቲያኑን ቀደሳት፤
በዓለት ላይ መሠረታት።
ከመከራ
በኃይሉ ድል ሰጣት።
ቅዱስ . . .።
፬፡ በቅዱስ ደሙ የዳኑ፤
የድል መዝሙር ሊዘምሩ፥
ለሱራፌል ይመልስ
ኪሩቤል።
ቅዱስ . . .።