Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 59 ክርስቶስ ሕያው ሆነ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ክርስቶስ ሕያው ሆነ፤ መቃብር በራ።
መድኃኒት ተገኘ፥ ትንቢትም ሞላ።
ግርማን ተጐናጽፎ ከሞት ተነሣ
ጠላት ተሸነፈ የሱስ ድል ነሣ።
ማኅተሙ ተፈት፥ ደንጊያው ለቀቀ፤
ጠባቂው ፈርቶ ፈጥኖ ሸሸ፤
ሲኦልም ተገዛ፥ ሃሌ ሉያ።
፪፡ ከጨለማ ጋር ብርሃን ሲዋጋ፥
ብርሃን ለዘላለም ፍጹም ድል ነሣ።
ያ ሞት ተደባየ፤ ድል ነሣ ሕይወት
ተስፋችን በረታ ለማጽናት እምነት።
እናንት ኀዘንተኞች ከልብ ተቀኙ፤
ከሞት አዳነነ በቸርነቱ፤
ሊኖር ከኛ ጋራ ሃሌ ሉያ።
፫፡ ሰማይ ከምድራችን አሁን ታርቆአል
መቃብር የደስታ መንገድ ሆኖአል።
በመስቀል ትይዩ ያለቀሳችሁ፥
ሞት ተሸንፎአል ደስ ይበላችሁ።
ከዘላለም ሕይወት የጠፉት ሁሉ፥
ወደ ቸር እረኛ ይመለሳሉ።
ሕይወት ያገኛሉ ሃሌ ሉያ።
፬፡ ቤተክርስቲያን ጸናች ነፍሳትም ይምጡ፤
በብርሃኑ ፍጥነት ሰፋ ትምህርቱ።
በዓለሙ ወጡ መልእክተኞቹ፤
ሞት እንኳ ሳይፈሩ ወንጌል ሊሰብኩ።
ስለኛ ለሞተ ነጻ ላወጣን፥
ምስክር ሊሰጡ ሰውን ለማዳን።
ሊጣሩ በደስታ ሃሌ ሉያ።
፭፡ ለምን ታዝናላችሁ እናንተ ምእመናን
አጭር ነው ዘመኑ ሞት እስኪጠራን።
መሬት እንደ እናት ልታቅፋችሁ፥
እንደ ሕያው ዘር ግን ቶሎ ልትወጡ።
የዘራው ይመጣል በመከር ጊዜ፥
እንክርዳዱን ሊለይ ከጥሩ ፍሬ።
ስንዴውን ሊያመርት ሃሌ ሉያ።