Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 321 እንግዳ ስደተኛየም እንዳባቶቼ ነኝ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ እንግዳ ስደተኛየም እንዳባቶቼ ነኝ፤
ቤቴም በላይ ነው እንጂ
በዚህ ዓለም አይገኝ።
በላይ ግን ቸር አባቴ
ቤቱን ከፍቶልኛል፤
እኔም ከእርሱ ጋር
መኖር እመኛለሁ።
ግሩም፥ ግሩም ነው ተስፋዬ፤
ወዲያ ስመለከት ይግላል ደስታዬ፤
፪፡ ስለኔ ሞትን ቀምሶ
ከሞትም ያዳነኝ፥
ቸር ወዳጄን የሱስን በዚያ ልገናኝ።
አስደሳች ነገር ሁሉ
በምድር ባገኝም፥
ወዲያ ግን ወደርሱ
ናፍቆት አይለቀኝም።
ግሩም፥ ግሩም ነው . . .።
፫፡ ኃጢአት በምድር ላይ
ሁሉን አረከሰ፤
እንደ ውኃ ሙላትም
ሁሉን አደረሰ።
ባያስፈርድብኝ እንኳ፥
ሰላም ይነሣኛል፤
ወዲያ ግን ስገባ ፍጹም ይለቀኛል።
ግሩም ግሩም ነው . . .።
፬፡ ልቆይ ልታገስ ገና
አይቀርም ተስፋዬ፤
ሊወስደኝ ወደ እርሱ
ይመጣል የሱሴ።
አሁን በእምነት ብቻ
ያለኝን ንብረቴን፥
ይሰጠኛል በሙሉ ስደርስ ወዳገሬ።
ግሩም ግሩም ነው . . .።