Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 302 የሱስ የነፍሴ ወዳጅ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የሱስ የነፍሴ ወዳጅ፥
ወደ እቅፍህ ልብረር።
ባሕሩ ሲናወጥብኝ፥
ወጀቡም ሲያንገላታኝ፥
መድኃኒቴ ከልለኝ፤
የሕይወት ማዕበል እስኪያልፍ።
በመጨረሻም፥ ነፍሴን
ወደ መንግሥትህ አግባት።
፪፡ ሌላ አምባ የለኝም፤
ነፍሴ የምትድንበት።
አዳኜ ሆይ አጽናናኝ፤
ብቻዬን አትተወኝ።
እምነቴ ባንተ ላይ ነው፤
እርዳታህን እሻለሁ።
ተከላካይ የለኝም፤
ጠብቅኝ በክንፍህ ስር።
፫፡ ክርስቶስ አንተን እሻለሁ፤
ሁሉ ካንተ ይገኛል።
የወደቁትን አንሣ፥
ደካሞችንም አጽና።
አንተ ፍጹም ቅዱስ ነህ፤
የኔ ልብ ግን እርኵስ ነው።
ክፋት የከበበኝ ነኝ፤
በኃጢአት የተሞላሁ።
፬፡ በሽተኞችን ፈውስ፤
ዕውሮችንም ምራ።
ድሆችህን ተመልከት፤
ችጋረኞችን ስማ።
በጸጋና በእውነት
የተሞላህ ቸር አምላክ፥
ወደ አንተ ሲማልዱ
ጌታ ሆይ ቅረባቸው።
፭፡ ካንተ ጸጋ ይገኛል።
ኃጢአቴን የሚሸፍን
ፈዋሽ ወንዝ ካንተ ይጕረፍ፤
ልቤንም ይጠብልኝ።
የሕይወት ምንጭ አንተ ነህ፤
ካንተ በነጻ ልውሰድ።
በልቤ ውስጥ ና ፍለቅ፤
ለዘላለም ንገሥ።