Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 295 የሱስ ክርስቶስ ወንድሜ ሆነልኝ የዘፈን ግጥሞች
፪፡ የሱስ ክርስቶስ ወንድሜ ሆነልኝ፤
ከእርሱም ጋር የምወርስ ነኝ።
ኀዘን ሁሉ ከኔ ይራቅልኝ፤
ፍጹም የለም የሚያስጨንቀኝ።
፪፡ አምላካችን አባቴ ሆነልኝ
ነገሩ እንዴት ያስገርማል?
ለአእምሮዬም ባይታይልኝ፥
ቃሉ ፈጽሞ ያስረዳኛል።
፫፡ እርሱ አምላኬና አምላካችሁ
አባቴም የናንተ አባት ነው፤
የኔ ወንድሞች እናንተ ናችሁ
ሲል፥ ተስፋዬ በርሱ ሙሉ ነው።
፬፡ እንደ ምኞቴ እንኳ ባይሰማኝ፥
ከቶ የርሱ ቃል አይፋለስም።
ነፍሴ ሆይ ይህን ተስፋ ስታገኝ፥
በእርሱ ደስ ይበልሽ በጣም።
፭፡ በሰው ሐሳብ ከቶ የማይመዘን
ግሩም የሆነ ወንድምነት ነው።
የሱስ ክርስቶስ በሚወርሰው መጠን
ርስቴም ከርሱ ጋር እኩል ነው።
፮፡ በመሞቱ የተከፈተልኝ
መንግሥቱም ይቆየኛል በላይ።
አምላኬ ሕዋሳቴን አብራልኝ
ርስቴንም ለእምነቴ አሳይ።