Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 292 የሱስ እኔን ተቀበለኝ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የሱስ እኔን ተቀበለኝ
ዞትር ተከባከበኝ፤
ጉድለት እንኳን ቢኖርብኝ፥
ለዘላለም ያንተ ነኝ።
ሕይወትና ኃይል አጣለሁ
እውድቃለሁ ሁሉ ቀን።
ባንተ ብቻ ተጥያለሁ
ከእናቴ ማኅፀን።
፪፡ እኔ አንድ ምስኪን ድኃ ነኝ፤
አንተ ሀብታም ጌታ ነህ።
አንተም ከመሞት አዳንኸኝ
ቅጣቴን ተቀብለህ።
ኃጢአቴም ቢያስፈራኝ፥
ዓይኔን ወደ አንተ ሳብ
አንተ ከርሱ ልታጠራኝ
አፍስሰሃል የደም ላብ።
፬፡ የሱስ ሆይ የሠራህልኝ
ለዘላለም በቂ ነው፤
ሕግህም እንዳይፈርድብኝም፥
አንተ ራስህ ፈጸምኸው።
አንተ ስትነግረኝም፥
አምኜ ልቀበለው።
ሌላ አያስፈልገኝም፥
ጸጋህን ላመስግነው።