Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 286 ጽናት በየሱስ እጆች የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ጽናት በየሱስ እጆች
እረፍትም በክንዱ
ደስታም በፍቅሩ ጥላ
ባገኝ ይበቃኛል።
በሰማያዊ አገር
ቅዱሳን መላእክት ሁሉ
ላምላክ ይዘምራሉ
በደስታ ሁሉ ቀን።
ጽናት በየሱስ እጆች
እረፍትም በክንዱ
ደስታም በፍቅሩ ጥላ
ባገኝ ይበቃኛል።
፪፡ ጽናት በየሱስ እጆች
ረድኤት በኀዘንም
ዓለም እኔን ቢፈትን
ኃጢአት አይገዛኝም።
ጥርጣሬ ሆነ ኀዘን
የሚያስፈራ ሁሉ
ለጥቂት ጊዜ ብቻ
እኔን ያሠቃያል።
ጽናት በየሱስ እጆች
ረድኤት በኀዘንም
ዓለም እኔን ቢፈትን
ኃጢአት አይገዛኝም።
፫፡ የሱስ የኔ አዳኝ ነው
ስለኔ ሞቶአል።
የሱስ ነው የኔ አምባ
በእርሱ እጽናናለሁ።
ስለዚህም ልታገሥ
ጨለማው እስኪያልፍ ድረስ
ወዲያ እስክደርስም
ቀን ወደ አለበት።
የሱስ የኔ መጽናናት
ስለኔ ሞቶአል
የሱስ ነው የኔ አምባ
በእርሱ እጽናናለሁ።