Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 28 የሱስ ለዓለም ሲል ሞቶአል የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የሱስ ለዓለም ሲል ሞቶአል፤
አምላኬ ሆይ ስጠኝ ማስተዋል።
ጌታ በመስቀል ሞተ ለኔ፤
እንዲያድነኝ ከኩነኔ።
፪፡ እንዴት ይገርማል ታላቅ ፍቅሩ፤
ማንም አይወደኝ እንደ እርሱ።
እርሱ ካዳነኝ በመሞቱ፥
ሕይወቴን ልስጠው ለክብረቱ።
፫፡ አምላኬ ሆይ ልጅህ አድርገኝ
ከሰይጣን ወጥመድ ሁሉ ፍታኝ።
አንተን ልከተል አስተምረኝ
ላንተም ልሆን በፍቅርህ እርዳኝ።