Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 234 የሱስ ሆይ የልቤ ተስፋ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የሱስ ሆይ የልቤ ተስፋ
ና ና ነፍሴን ደስ አሰኝ።
ደግፈኝ በአንተ ጸጋ
በቃልህ ብርሃን ሁነኝ።
ና ወደኔ የሱስ ሆይ
ከኔም ዘንድ ዘወትር ቆይ።
፪፡ በቅዱስ ስምህ ልጀምር
ዕለት ዕለት ሥራዬን።
በረከት በላዬ ጨምር
እስክፈጽም ዕድሜዬን።
ና ወደኔ . . .።
፫፡ ያፌን ቃል የልቤን አሳብ
በምሕረትህ እይልኝ።
ነዋሪ ሀብት ለመሰብሰብ
ሁልጊዜ አነቃቃኝ።
ና ወደኔ . . .።
፬፡ ቀን አልፎ ሌሊት ሲተካ
ጠብቀኝ ቸሩ ጌታ።
አትራቅብኝ ሲነጋ
የሱስ ሁን ከኔ ጋራ።
ና ወደኔ . . .።