Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 211 ያንተን ሰላም የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ያንተን ሰላም
ኦ የሱስ አውርድልን
በሁከት የሚያድል ጸጥታን።
በእንግድነት ተስፋን የሚሰጠን
ለገነት የሚለውጥ በረሃን።
፪፡ ላጭር ጊዜ
ከዓለም ጋር ስታገል
አይዞህ ልጄ ብለህ አጠንክረኝ።
ላጭር ጊዜ ልዝራና ላገልግል
የመከሩ ቀን እስኪነጋልኝ።
፫፡ ላጭር ጊዜ
ይሆናል ሥቃይ ኀዘን
ነፍሳችን በዚህ ዘወትር ይጾማል።
ወዲያ ግን ደስታና ትርፍ ሊቆየን
ከሕይወት ወንዝ ነፍሳችን ይረካል።
፬፡ ባጭር ጊዜ
አንተ እስክትመጣ
መብራቴን አብርቼ ልጠብቅህ።
ስትመጣ ሊሆነኝ ደስታ እልልታ
ሁልጊዜ ምስጋና ይሁንልህ።