Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 171 የሱስ ሆይ ቃልህ ጽኑ ነው የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የሱስ ሆይ ቃልህ ጽኑ ነው
መንግሥትህ የማይፈርስ ነው።
ጠላቶች ቢነሡብህም
ወዳምባህ ግን አይደርሱም።
እስከ ዘላለም እንዳይወድቅ
አንተ በውነትና በጽድቅ
ዙፋንህን አጸናህ።
፪፡ ለእኛ ግን የሚጠፋ
የሚያልፍ ይመስለናል።
መንግሥትህ ግን እንደ ጸና
ለዘላለም ይኖራል።
ይህንንም እንድናምን
የማስተዋልን ኃይል ስጠን
በመንፈስህም አበርታን።
፫፡ የሱስ ክርስቶስ ያንተ መንግሥት
ከዚህ ዓለም አይደለም
ከዓለም ጠቢባን ሁሉ
የሚያምኑህ ባይኖሩም
ተከታዮችህ ምእመናን
የዋጀሃቸው ቅዱሳን
ይሰግዱልሃል ባለም።
፬፡ ጌታ የሱስ ሆይ ተመስገን
በጸጋህ ስላዳንኸኝ።
ዘላለማዊ መንግሥትህን
ወራሽ ስላደረግኸኝ።
ለአንተ ክብር ምስጋና
ልዘምር ነው በደስታ
በሰማይ በብፅዕና።