መዝሙር 494 መዳኔን ላውጅ እወዳለሁ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ መዳኔን ላውጅ እወዳለሁ
በሞተው በግ ደም ድኛለሁ።
ወሰን በሌለው ምሕረት ዳንኩኝ፥
ለዘላለምም ልጁ ነኝ።
ዳንኩኝ ዳንኩኝ በጌታዬ ደም ድኛለሁ
ዳንኩኝ ዳንኩኝ ለዘላለምም ልጁ ነኝ።
፪፡ ዳንኩኝ በኢየሱስ ደስታ አለኝ
ቋንቋ ሊነግረው የማይችል።
አውቃለሁ የጌታዬ ብርሃን፥
ዘወትር ከኔ ጋር ይኖራል።
ዳንኩኝ ዳንኩኝ . . .።
፫፡ ብሩክ አዳኜን አስባለሁ
እርሱን ሳስብ እውላለሁ።
ያለ እረፍትም እዘምራለሁ፥
ፍቅሩም የመዝሙር ዜማ ነው።
ዳንኩኝ ዳንኩኝ . . .።
፬፡ ሕጉ የሚያረካኝን ንጉሥ
በክብር እንዳየው አውቃለሁ።
በፍቅሩ ነፍሴን ይጠብቃል፥
መዝሙር በሌት ይሰጠኛል።
ዳንኩኝ ዳንኩኝ . . .።
፭፡ ዘውድ እንሚቆየኝ አውቃለሁ
በዚያ በሚያበራው ስፍራ።
ፍጹም ከሆነው መንፈስ ጋራ፥
በጌታ ቤት እኖራለሁ።
ዳንኩኝ ዳንኩኝ . . .።