መዝሙር 438 አንዲት ከተማ አየሁ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አንዲት ከተማ አየሁ
ማንም ያላያትን፥
ውበትዋ ዕፁብ ድንቅ ነው
ሌሊት የለባትም፥
ብርሃንዋ የሱስ ነው፥
ለዘላለም የሚያበራላት።
እመኛለሁ እመኛለሁ፥
በዚያች ከተማ ውስጥ ለመኖር።
እመኛለሁ እመኛለሁ፥
ከጌታ ከየሱስ ጋራ ለመሆን።
፪፡ ከከተማው መሐል
ከበጉ ዙፋን ሥር፥
የሚወጣ የሕይወት ምንጭ አለ።
ለሚጠጡት ሁሉ፥
ሕይወትን ይሰጣል፥
ዳግመኛ መጠማት አይኖርም።
እመኛለሁ . . .።
፫፡ ከዚህ ዓለም ስለይ
ዘመኔን ጨርሼ፥
ችግርና ስቃዬም ቀርቶ።
በዚያች ከተማ ውስጥ፥
ለነገሠው ንጉሥ፥
ለዘላለም እዘምራለሁ።
እመኛለሁ . . .።