መዝሙር 356 ደካሞች የሱስ ሲጠራችሁ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ደካሞች የሱስ ሲጠራችሁ ስሙ።
ሸክማችሁም የከበደ ሁሉ፥
ኑ ለዘላለም ዕረፍትን ልስጣችሁ፥
ችግራችሁንም ላቅልልላችሁ፥
ኑ ወደኔ ከእኔ ተማሩ፥
ቀንበሬ ልዝብ ነው፥
ሸክሜም ቀሊል ነው።
የዋህ ነኝ ትሑት ነኝ፥
በእኔ እመኑ፤
ኑ ላሳርፋችሁ፤
ኑ ልባርካችሁ።
፪፡ በኀዘን የተጨነቃችሁ ሁሉ፥
ጥርጥርና ሐሳብ ያጠቃችሁ፥
ችግራችሁን ለየሱስ ንገሩ፥
ጭንቃችሁንም ለርሱ አስረክቡ።
ኑ ወደኔ . . .።
፫፡ ፈተና ማሸነፍ የተሳናችሁ፥
ሕይወታችሁ የተዳከመባችሁ፥
ኑ ወደ የሱስ፥ ኃይል እንደታገኙ፥
በመንፈስ ቅዱስ እንደትታደሱ።
ኑ ወደኔ . . .።