መዝሙር 347 ዳግም ያልተወለደ ላዲስ ሕይወት የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ዳግም ያልተወለደ ላዲስ ሕይወት
ያምላክን መንግሥት አያይም፤
ክርስቶስን ያልያዘ በልብ ሃይማኖት፥
ወደ ሰማይም አይገባም።
ደጁ ጠባብ ነው ተጋደል ለመግባት፥
ቀንም አጭር ነች እንዳታባክናት።
ልትጥር ያስፈልግሃል በትጋት፥
እንዳይቀርብህ ብፅዕናው።
፪፡ ሰምተህ ከመዳን ይከለክልሃል
ሰይጣን ያ ክፉ ጠላትህ፤
ባለም ደስታ ሁሉ ያታልልሃል፥
እንዳትድን ከጥፋትህ።
ምክሩን አትስማ ፍራው ወዳጄ ሆይ፥
ካለም ተንኰል ራቅ በዚያ አትቆይ፤
ንስሐ ለመግባትም አትዘግይ፥
የሱስ በፍቅር ሲጠራህ።
፫፡ በሰማይ ለጻርህ ለትግልህም
ምን ያህል ውሮታ አለህ፤
ወዲያም ከደረስህ አይጸጽትህም፥
አክሊልህን ታገኛለህ።
ስለዚህ ተነሥ በፍጥነት ተዘጋጅ፥
ጌታ ሳይመለስ የዓለሙ ፈራጅ፤
የሰርግ ልብስ ያልለበሰ በሰማይ ደጅ
እስከ ዘላለም አይገባም።
፬፡ እውነተኛ እምነት በልብህ ባይገኝ
ወደ ሰማይ አትደርስም፤
የክርስቶስን ጽድቅ ልትለብስ ባትመኝ፥
ሕይወትንም አትወርስም።
የምትድነው በእምነት ብቻ ነው፥
የክርስቶስን ጽድቅ አሁን ተቀበለው፤
የሱስም በፍቅር ሲጠራህ ስማው፥
እርሱን የሰማ ይድናል።
፭፡ የሕይወትን ዘውድ እንዲያገኝ በእምነት
ዓለሙ ሁሉ ተጠራ፤
ላንተም ዘውድ ተዋጀ በኢየሱስ ሞት፥
ለአንተ በፍቅሩ ራራ።
ታላቁ ጌታ እጅግ ያዝንልሃል፥
እጆቹን በፍቅር ዘርግቶልሃል፥
ከእንቅልፍህም ይቀሰቅስሃል፥
ብፁዕ ነህ ብትነቃለት።