መዝሙር 341 ሁሉን ለየሱስ ሰጥቼ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ሁሉን ለየሱስ ሰጥቼ
ነፍሴን አስረክባለሁ
ለዘላለም አምነዋለሁ
በፊቱም እጸናለሁ።
ሁሉን ላስረክብ ሁለመናዬን
ለተባረከው አምላኬ
ነፍሴን ላዳንኸው።
፪፡ ሁሉን ለየሱስ ላስረክብ
በትህትና ልንበርከክ
ዓለማዊ ደስታ ይጥፋ
የሱስ ሆይ ተቀበለኝ።
ሁሉን ላስረክብ . . .።
፫፡ ሁሉን ለየሱስ ላስረክብ
አዳኜ ፍጹም አርገኝ
መንፈስህ በውስጤ ይስረጽ
የኔ መሆንህን ልወቅ።
ሁሉን ላስረክብ . . .።
፬፡ ሁሉን ለየሱስ ላስረክብ
ሕይወቴም የእርሱ ይሁን
በፍቅርህ በኃያል ክንድህ
በበረከትህ ሙላኝ።
ሁሉን ሰላስረክብ . . .።