Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 322 ካለም መሄዴ ይደርሳል የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ካለም መሄዴ ይደርሳል፤
እንዳሁንም አልዘምርም።
ግን ወዳምላኬ ቤት ስገባ፥
ደስታዬ እጅግ ይበዛል።
ፊት ለፊትም አየዋለሁ፤
የጸጋው ታሪክም ይህ ነው።
ፊት ለፊትም አየዋለሁ፤
በጸጋው ነው ያገኘሁት።
፪፡ ምድራዊ ቤቴ ይፈርሳል፤
ቀኑን ሳላውቀው ብቀርም፥
ይህንን ግን አውቀዋለሁ፥
ቦታ እንዳለኝ በሰማይ።
ፊት ለፊትም . . .።
፫፡ የፀሐይ ብርሃን ይጠፋል፤
ያሁን ድምቀቷ ይቀራል።
ያን ጊዜ ጌታ ይለኛል፥
ታማኝ ባሪያ አሁን ዕረፍ።
ፊት ለፊት . . .።
፬፡ መብራቴን አብርቼ ቀኑን
መጠበቅ ብቻ አለብኝ።
መድኃኒቴ በሩን ሲከፍት፥
ነፍሴ ባምላኬ ታርፋለች።
ፊት ለፊት . . .።