መዝሙር 78 ተነሥቶአል – ክርስቶስ – ተነሥቶአል የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
ተነሥቶአል – ክርስቶስ – ተነሥቶአል
ተነሥቶአል – ክርስቶስ – ተነሥቶአል
ተነሥቶአል – ክርስቶስ – ተነሥቶአል
ተነሥቶአል – ተነሥቶአል- ተነሥቶአል
ለምን ሕያውን ከሙታን ትፈልጉታላችሁ
ተነሥቶአል – ክርስቶስ
ተነሥቶአል ተነሥቶአል
ሰላም – ሰላም ሰላም – ለናንት
ሙቶ ነበረ ዛሬም ለወደፊትም ሕያው ነው።
ለዘለዓለም – ለዘለዓለም
ለዘለዓለም – ለዘለዓለም።
ሞት ሆይ፥ ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ
ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሳትህ የት አለ
በሞቱ ሕያዋን ሆነናል አብረን ከክርስቶስ ጋር
አብረን ከርሱ ጋር
እግዚአብሔር ሕያዋን አድርጐናል።
አብረን ከክርስቶስ ጋር ከክርስቶስ
አብረን ከክርስቶስ ጋር እንድንኖር
በሰማይ ስፍራ አዘጋጀልን
እንግዲህ አብረን እንግዲህ አብረን
ከተነሣን ከእርሱ ጋር
ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ
ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እንሻ
አላፊ የሆነውን ምድራዊውን ትተን
ሰማያዊውን እንፈልግ
ክርስቶስ መድኃኒታችን ሲገለጽ ሳለ
እኛም ከእርሱ-ጋር-አብረን ጋራ በክብር
ከእርሱ – ጋር – እንገለጻለን።
ይመለሳል – አዎን፥ ይመለሳል
አዎን፥ ይመለሳል – ይመለሳል
ይመለሳል – ይመለሳል።