መዝሙር 565 ተስፋ ቍረጥ ሰይጣን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ተስፋ ቍረጥ ሰይጣን
እኔን አትፈትነኝ፤
ተስፋ ቍረጥ።
በጣም የሚያጽናናኝ
ጠባቂ እራኛ አለኝ፤
ተስፋ ቍረጥ።
፪፡ ተስፋ ቍረጥ ሰይጣን
አትምጣ ወደኔ፤
ተስፋ ቍረጥ።
ያለም ሁሉ አዳኝ
ነውና መድኅኔ፤
ተስፋ ቍረጥ።
፫፡ ተስፋ ቍረጥ ሰይጣን
መከራ አታከማች
ተስፋ ቍረጥ።
የኔ አምባ የኔ ኃይል
አይደለም ሟች፤
ተስፋ ቍረጥ።
፬፡ ተስፋ ቍረጥ ሰይጣን
ወንጌሉ ተዘራ፤
ተስፋ ቍረጥ።
ነፍሳት አመለጡ
ከገሃነም መከራ፤
ተስፋ ቍረጥ።
፭፡ ተስፋ ቍረጥ ሰይጣን
አትችልም ልትይዘኝ።
ተስፋ ቍረጥ።
በጌታ በየሱስ
በደሙ ውስጥ ነኝ፤
ተስፋ ቍረጥ።
፮፡ ተስፋ ቍረጥ ሰይጣን
ኢትዮጵያችን ዳነች፤
ተስፋ ቍረጥ።
የወንጌልን ቃል
በመመገብ ላይ ነች፤
ተስፋ ቍረጥ።
፯፡ ተስፋ ቍረጥ ሰይጣን
ነፍሳት ተከማቹ፤
ተስፋ ቍረጥ።
የየሱስ አዳራሽ
ስለ ሆነ ምቹ፤
ተስፋ ቍረጥ።