መዝሙር 529 ስብሐት ለእግዚአብሔር የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ስብሐት ለእግዚአብሔር
ስብሐት ለአንድ ልጁ፤
ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ስም
ካሁን እስከ ዘላለም።
ሳናውቀው አወቀነ፥
ሳንወደው ወደደነ።
ሳንሻው ፈለገነ
ልጆቹ ልንሆን።
፪፡ ርኅሩኅ አባት ከሰማይ
አየን አሽቈልቍሎ፥
በዓለም እድፍም ተውጠን
ጠፍተንም ተባርረን።
ኃጢአታችን ሸፍኖን
ርኩሰትም አሸንፎን፥
ወገኖቹም ተጨንቀው፥
መድኃኒት አጥተው።
፫፡ ተስፋ ተሰጥቶን ነበር
ያም ተስፋ ቃል ነበር።
ነቢያት ያስጠነቀቁት
የመምጣቱን ነበር፥
በሰው ፈቃድም ሳይሆን
ግን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል
ሰው ሆነ ሥጋ ለብሶ
ባለም ተገለጠ።