መዝሙር 482 ንቁ ቁሙ ለየሱስ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ንቁ ቁሙ ለየሱስ
እናንተ ወታደሩ፤
የጽድቁን ጥሩር ልበሱ፣
በእርሱ ተመሩ።
ጠላት ሁሉ እስኪሸነፍ፥
እርሱ ሊረዳችሁ፤
ከድልም ወደ ድልም፥
በርሱ ታምናላችሁ።
፪፡ ንቁ ቁሙ ለየሱስ
ጌታን ተመልከቱ፤
ከላይ ከሰማይ ሲታይ፥
በደመቀ ፊቱ።
ተነሥተን እንገናኝ፥
በላይ በደመና፤
በእርሱ ደስ ይበለን፥
አምባችን ነውና።
፫፡ ንቁ ቁሙ ለየሱስ
በብርታቱ ቁሙ፤
የሥጋ ክንድ አይችልም፥
በጨለማ ዓለም።
ስለዚህ ልትድኑ፥
በፈሰሰው ደሙ።
ወንጌልንም ልበሱ፥
ትእዛዙንም ስሙ።
፬፡ ንቁ ቁሙ ለየሱስ
እናንተ ሎላልቱ፤
ዛሬ በዘመቻ ቀን፥
ለድላችሁ ብርቱ።
በእርሱ የሚያሸንፍ፥
ሊኖር በመንግሥቱ
ተስፋ ተደርጐለታል
በሰማይ ርስቱ።