መዝሙር 477 አምላካችንን እናመስግን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አምላካችንን እናመስግን
ከዘላለም የነበረውን።
ልኮልናልና ታላቁን መድኀን
ከኃጢአታችን ያነጻንን።
ታጥቀን እንገስግስ
ታጥቀን እንገስግስ።
የሃይማኖትን ዘውድ ተቀዳጅተን
የመንፈስንም ሰይፍ ጨብጠን።
፪፡ የሃይማኖት ጋሻ መክተን
የሰላምን ጫማ አድርገን።
የአምላክን የጽድቅ ጥሩር ለብሰን
በእውነት ሰቅ ወገባችንን ታጥቀን።
ታጥቀን እንገስግስ
ታጥቀን እንገስግስ
እንደ አምላካችን ቃል ጽድቁን ለብሰን
የመንፈስን ጫማ አድርገን።
፫፡ ስንደክም ቤታችን እንዳይፈርስ
ምን ይዘን እንሂድ ለኢየሱስ።
ለኛ ሲል ተዋርዶ እስከዚህ ድረስ
ደሙን እንደ ውኃ ሲያፈስ።
ታጥቀን እንገስግስ
ታጥቀን እንገስግስ።
የሃይማኖትን ዘውድ ተቀዳጅተን
የመንፈስንም ሰይፍ ጨብጠን።