መዝሙር 465 መልካሙን ሥራ የሚሠራ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ መልካሙን ሥራ የሚሠራ
ወደ ጌታ ፍቅር የሚጠራ።
በመዝሙረ ቃና በምስጋና፥
ቀኑን በደስታ የሚያበራ።
ያ ሰው አንተ ነህ ወይ(2)
፪፡ በሕይወት ጸጋ የሚደሰት
በመልካም ፈቃድ የሚለግሥ።
ለውነት የቆመ በጀግንነት፥
ለተቸገሩ ፈጥኖ ደራሽ።
ያ ሰው . . .።
፫፡ ምፅዋት ቸርነትን የሚወድ
ሸክም የከበደውን የሚያግዝ።
የክርስቶስን ፍቅር የሚያበሥር፥
ቤዛነቱን የሚመሰክር።
ያ ሰው . . .።
፬፡ ኀዘንተኛውን የሚያጽናና
የወንጌልን ቃል የሚዘራ።
በፍቅር በሰላም የሚኖር
በእምነት የጸና ከአምላክ ጋር።
ያ ሰው . . .።