መዝሙር 447 የአምላክ ቃል ያሸንፋል የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የአምላክ ቃል ያሸንፋል
የጨለማውን ጭፍራ፥
ክፉ ቅናት ሰይፍ ወይም እሳት፥
ወንጌሉን አያስቀርም።
፪፡ ባምላክ ትእዛዝ ሰባኮቹ
በመላ ዓለም ወጡ፤
ለማስተማር ቅዱስ ቃሉን፥
ሕይወት የሚሰጠውን።
፫፡ ለጨካኞች ላመፀኞች
ወንጌልን ይሰብካሉ፤
በጨለማ እንዲበራ፥
ብርሃኑን ያቆማሉ።
፬፡ ሕያው ቃሉ ያጸናናል
ለተጨነቁ ሁሉ፤
ለአዘኑ ሰላም ላጡ
ጽኑ ተስፋ ይሰጣል።
፭፡ በዓለሙ ይዘራሉ
አምላክ ቃሉን ያለማል፤
በምሕረት ቀን እንድ ነፍስ ቢድን፥
አምላክን ደስ ያሰኛል።
፮፡ ልዑል ንጉሥ በኛ ንገሥ
ግዛትህንም አስፋው፤
ድል ያንተ ነው በዓለሙ፥
ላንተ ይሁን ምስጋና።