መዝሙር 427 የሱስ ነው የእኔ ተስፋ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ ነው የእኔ ተስፋ
ሞትን ድል ነስቶ ተነሣ፤
እውነትን ተረዳሁኝ፥
ኀዘንም ትካዜም ጠፋ።
የሞት ሌሊት ይነጋል፥
ጨለማውም ይጠፋል።
፪፡ ሕያው ነው መድኃኒቴ
እኔ ሕይወትን እንድወርስ፥
ይተባበራል ከኔ።
ሰበብ የለኝም ለማልቀስ፥
ቸር አባት ከፍቶ ቤቱን፥
ይቀበላል ልጆቹን።
፫፡ ከእርሱ ጋር ልተባበር
በእምነት ጸንቼ ልኑር።
በሕይወት ቢሆን በሞት፥
ጽኑ ብፁዕ ተስፋ አለኝ።
ከጌታ የሚለየኝ፥
አንድ እንኳ ባለም አይገኝ።
፬፡ ከንቱ ሥጋ ነኝና
ወደ መሬትም ልመለስ፤
ያስነሣኛል ግን ጌታ፥
ክቡር መንግሥቱን እንድወርስ።
ከመድኃኒቴ ጋራ፥
ልነግሥ ነው በብፅዕና።
፭፡ በሽታ ያማቀቀው
ድኖ በሰማይ ይኖራል፤
በውርደት የተዘራው፥
ቆይቶ በክብር ይነሣል።
የምድሩ ሕምሕምታ፥
ይለወጣል በዕልልታ።
፮፡ በደስታ ዘምሩ
የሱስ ልጆቹን ይጠራል፤
ሰዎች ሞትን አትፍሩ፥
ብንሞትም ያስነሣናል።
ሙታን ድምፁን ሲሰሙ፥
ከመቃብር ሊወጡ።
፯፡ ከከንቱ ዓለም ራቁ
በእርሷም አትታለሉ፥
እንድትሞቱ በተስፋ
በሰማይ ያለውን እሹ።
ብትመኙ ብፅዕና
አሁን ሁኑ ቅዱሳን።