መዝሙር 398 የሱስ ክርስቶስ ወንድሜ ሆነልኝ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ ክርስቶስ ወንድሜ ሆነልኝ
ከእርሱም ጋር የምወርስ ነኝ።
ኀዘን ሁሉ ከኔ ይራቅልኝ፥
ፍጹም የለም የሚያስጨንቀኝ።
፪፡ አምላካችን አባቴ ሆነልኝ
ነገሩ እንዴት ያስገርማል።
ለአእምሮዬ ባይሰማኝም፥
ቃሉ ፈጽሞ ያስረዳኛል።
፫፡ እርሱ አምላኬና አምላካችሁ
አባቴም የናንተ አባት ነው።
የኔ ወንድሞች እናንተ ናችሁ፥
ሲል ተስፋዬ በርሱ ሙሉ ነው።
፬፡ እንደ ምኞቴ እንኳ ባይሰማኝ
ከቶ የርሱ ቃል አይፋለስም።
ነፍሴ ሆይ፥ ይህን ተስፋ ስታገኝ፥
በርሱ ጸጋ ደስ ይበልሽ በጣም።
፭፡ በሰው ሐሳብ ከቶ የማይመዘን
ግሩም የሆነ ወንድምነት ነው።
የሱስ ክርስቶስ የሚወርሰው መጠን፥
ርስቴም ከርሱ ጋር እኩል ነው።
፮፡ በመሞቴ የተከፈተልኝ
መንግሥቱም ይቆየኛል በላይ።
አምላኬ ሕዋሳቴን አብራልኝ፥
ርስቴንም ለእምነቴ አሳይ።