መዝሙር 391 አስደናቂ መድኅን ነው ኢየሱሴ ለኔ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አስደናቂ መድኅን ነው ኢየሱሴ ለኔ
አስደናቂ ነው መድኀኔ።
በአምባው ውስጥ ነፍሴን ይጠብቃታል
ከሕይወት ምንጭ ያጠጣታል።
በአምባው ውስጥ ነፍሴን
ይጠብቃታል
በጸጋው ይሸፍናታል
ነፍሴንም በጥልቅ ፍቅሩ ያረካታል
በእጁም ይከልላታል
በእጁም ይከልላታል።
፪፡ አስደናቂ መድኅን ነው ኢየሱስ ለኔ
ሸክሜን ሁሉ የሚያነሣ።
እንዳልሰናከል ይጠብቀኛል
በየቀኑ ያበረታኛል።
በአምባው ውስጥ . . .።
፫፡ በበረከቱ ያበለጽገኛል
አትረፍርፎ ይሰጠኛል።
ለእግዚአብሔር ክብር እዘምራለሁኝ
በምሕረት ለዋጀኝ መድኅን።
በአምባው ውስጥ . . .።
፬፡ በኢየሱስ ብርሃን ለብሼ ስነሣ
ልገናኘው በደመና።
የማዳን ኃይልና የርሱን ድንቅ ፍቅር
ልዘምር ከአእላፋቱ ጋር።
በአምባው ውስጥ . . .።