መዝሙር 340 ማዕበሉ ሲናወጥ ሲበዛ መከራ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ማዕበሉ ሲናወጥ ሲበዛ መከራ
ሕይወት ሲያስጨንቀኝ የዚህ ዓለም ሥራ።
የጌታን ድምፅ ሰማሁ ሲለኝ ጽና በርታ፥
ከቶ እደማይተወኝ ሰጠኝ ሙሉ ተስፋ።
ከቶ አይተወኝም ከቶ አይተወኝም፥(2)
ተ-ስፋው አጽንቶኛል ብቻዬን አይተወኝም።
፪፡ በጭንቀት ሸለቆ ውስጥ እርሱን ተመርኩዤ
መስቀሌ ሲከብድብኝ አለልኝ መድኅኔ።
ወዳጆቼ ሲተዉኝ ነፍሴ እንዳትፈራ፥
ከቶ እንደማይተወኝ ሰጠኝ ሙሉ ተስፋ።
ከቶ አይተወኝም . . .።
፫፡ በዚያ ኮረብታ ላይ ስለኔ ተሠዋ
እጆቹና እግሮቹ ጐኑም ላይ ተወጋ።
የመዳን ምንጭ ፈልቆ እኔን አንጽቶኛል
በክብሩ ዙፋን ላይ ነግሦ ይጠብቀኛል።
ከቶ አይተወኝም . . .።