መዝሙር 330 የሱስ ሆይ ቅዱስ እጅህ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ ሆይ ቅዱስ እጅህ
በእኔ ላይ ይስፈፍ፥
በኀዘንም በደስታም፥
በአንተ ዘንድ ልረፍ።
ጥበቤም ኃይሌም ጥጌም፥
ሁሉ በሁሉ ሁን።
እኔም በቀን በሌትም፥
በጸጋህ ውስጥ ልሁን።
፪፡ ስጠኝ ያንተን ይቅርታ
በደምህም አንጻኝ።
አግባልኝ ቅዱስ አሳብ፥
ፈቃድህም ይምራኝ።
ሁላችንንም ጠብቅ፥
መልአክ በዚህ ይስፈር።
አሁንም በሰላምህ፥
የሱስ ሆይ፥ እንደር።