መዝሙር 294 የሱስ ወደ ሄድህበት የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ ወደ ሄድህበት
ለመድረስ ናፈቅሁኝ
አይገኝም ሰላም እረፍት
ዓለም በሚሰጠኝ
አሳቤን የሚያድስ
ልቤን የሚቀድስ
አፍስስልኝ መንፈስህን
ጸጋህንም ስጠኝ።
፪፡ ፈተናን ለማሸነፍ
ክፉን ድል ለመንሣት
እኔን በኃይልህ ደግፍ
ጠብቀኝ ከኃጢአት።
ከጥፋት ልታድነኝ
በደስታና በኀዘን
ልከተልህ እርዳኝ።
፫፡ ከኃጢአት ተለይቼ
ጻድቅ ልሆንልህ
ቅዱስ ማጥሪያ ለኔ
ሰጠኸኝ በደምህ።
በሰማይ ርስት እንዳገኝ
በመስቀል ሞትህልኝ
ከመቃብር ተነሥተህ
ዐርገሃል በግርማህ።
፬፡ ብፁዕ ለመሆን ልመኝ
ከፍ ልል ከከንቱነት
በቸርነት ጠራኸኝ
ለዘላለም ህይወት።
ከዚህ ምድራዊ ውርደት
ሽቅብ ልመልከት
ወደዚያ ለመግባት
ልደራጅ በትጋት።
፭፡ ደግሞ እንዳይደልለኝ
ጠብቀኝ ከዓለም
ከክፉ ምኞት ለየኝ
ሕግህን ልፈጽም።
በኪዳንህ ጠብቀኝ
ምሕረትህን ስጠኝ
ነፍሴን በቡሩክ ስንብት
እስከምትጠራት።