መዝሙር 283 ክብር ለአምላክ ይሁን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ክብር ላምላክ ይሁን
የልመናችንን ድምፅ ሰምቶአልና፤
ጆሮውን ወደኛ አዘንብሎአልና፥
እናቅርብ ምስጋና ለቸር ጌታ።
፪፡ ምሕረቱ ብዙ ነው
ቍጣውም የራቀ ነው ከልጆቹ፥
ፍቅር ሰላም ረድኤት በጸጋው ሰጥቶናል፥
የመዳንን ተስፋ አውርሶናል።
፫፡ ምን እንመልሳለን
ላደረገው ሁሉ እግዚአብሔር?
ወንጌሉን እንመስክር ቃሉንም እንዝራ፥
ለተራበችው ነፍስ ይህ ነው ተስፋ።
፬፡ መሥዋዕት ምስጋና
እናቅርብ ለጌታ በመቅደሱ፤
በቤቱ እንስገድ በአደባባዩም፥
ስሙን እየጠራን ሃሌሉያ።