መዝሙር 273 የምሥራች ሰምተናል የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የምሥራች ሰምተናል
ኢየሱስ ያድናል።
ታሪኩን ተናገሩ፥
ኢየሱስ ያድናል።
ወንጌልን አሰራጩ፥
መከራን ሁሉ ቻሉ።
የጌታችን ፈቃድ ነው፥
ሰው ሁሉ እንዲድን።
፪፡ ታላቅ ጸጋ ተሰጠን
ኢየሱስ ያድናል።
ደስ ይበላችሁ ኃጥአን፥
ኢየሱስ ያድናል።
ልባችሁን ክፈቱ፥
የሱስንም አስገቡት።
ለጠላት ስፍራ ንሱት፥
ጌታችን እንዲነግሥ።
፫፡ ዙፋኑን ትቶ ወርዷል
ኢየሱስ ያድናል።
በሞቱ ሕይወት ሰጠን፥
ኢየሱስ ያድናል።
ደስ ብሏችሁ ዘምሩ፥
ለአምላክ ልጅ ለበጉ።
ድል ስለ ተገኘልን፥
እንዘምር ለአምላክ።
፬፡ ሃሌ ሉያ እንበል
ኢየሱስ ያድናል።
ሕዝቦች ደስ ይበላችሁ፥
ኢየሱስ ያድናል።
በደሙ ዛሬ ገዛን፥
ወደርሱ እንድንቀርብ።
ምሕረትን እንድንወስድ፥
ጸጋን እንድናገኝ።