መዝሙር 261 ምስጋና ምስጋና ለኢየሱስ ምስጋና የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
ምስጋና ምስጋና ለኢየሱስ ምስጋና
ይገባሃል አምላክ ላንተ ለሆንከው ገናና።
፩፡ መከራ እንደሚያልፍ የጊዜውም ኀዘን
እንደምንራመድ ሁሉን ነገር አልፈን።
ልቅሶ በዝማሬ ኀዘን በደስታ
እንደሚለወጡ ተናግሯል ያ ጌታ።
ምስጋና ምስጋና . . .።
፪፡ እንደ በደላችን አልተከፈለንም
ጌታ በመዓቱ አልተገናኘንም
ምሕረትን የሚወድ የሠራዊት ጌታ
ዕዳዬን ለመክፈል በውርደት ተመታ።
ምስጋና ምስጋና . . .።
፫፡ በኑሮዬ ሁሉ አንተን አስከብሬ
በመከራ ልለፍ ካንተ ጋር አብሬ።
የሕይወት እስትንፋስ ሰጥተኸኛልና
መሥዋዕቴ ይኸው ከነፍሴ ምስጋና።
ምስጋና ምስጋና . . .።
