Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 261 ምስጋና ምስጋና ለኢየሱስ ምስጋና የዘፈን ግጥሞች

መዝሙር 261 ምስጋና ምስጋና ለኢየሱስ ምስጋና የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009

 

ምስጋና ምስጋና ለኢየሱስ ምስጋና
ይገባሃል አምላክ ላንተ ለሆንከው ገናና።
፩፡ መከራ እንደሚያልፍ የጊዜውም ኀዘን
እንደምንራመድ ሁሉን ነገር አልፈን።
ልቅሶ በዝማሬ ኀዘን በደስታ
እንደሚለወጡ ተናግሯል ያ ጌታ።
ምስጋና ምስጋና . . .።
፪፡ እንደ በደላችን አልተከፈለንም
ጌታ በመዓቱ አልተገናኘንም
ምሕረትን የሚወድ የሠራዊት ጌታ
ዕዳዬን ለመክፈል በውርደት ተመታ።
ምስጋና ምስጋና . . .።
፫፡ በኑሮዬ ሁሉ አንተን አስከብሬ
በመከራ ልለፍ ካንተ ጋር አብሬ።
የሕይወት እስትንፋስ ሰጥተኸኛልና
መሥዋዕቴ ይኸው ከነፍሴ ምስጋና።
ምስጋና ምስጋና . . .።

Exit mobile version