መዝሙር 248 የሱስ ነህ የሕይወት ንጉሥ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ ነህ የሕይወት ንጉሥ
ለዘላለም የምትነግሥ
በሞትህ ኦ መድኃኒቴ
ተገኘልኝ ደኅንነቴ።
፪፡ ትንሣኤ ሕይወት እኔ ነኝ
ያልኸው ቃልህ ይታመናል።
በሙሉ ልቡ ያመነህ፥
ቢሞትም ሕይወት ያገኛል።
፫፡ መድኃኒቴ፥ ያለም ብርሃን
የምታበራ ጨለማን።
የምትመራኝ በብርሃንህ፥
የንጋት ኮከብ አንተ ነህ።
፬፡ ቃልህን አምኖ የሚቀበል
ጌታዬ አምላኬም የሚል
ብፁዕ ነው እርሱ ይድናል
ወደ ሕይወት ይሻገራል።
፭፡ ታላቅ አምላክ፥ ቸሩ ጌታ
ለሠራህልኝ ውለታ
ለስምህ ክብር ውዳሴ
ታቀርባለች ዘወትር ነፍሴ።