መዝሙር 245 ሰማያት የአምላክን ክብር የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ሰማያት የአምላክን ክብር
ይናገራሉ።
ፍጥረታት ሁሉ የጆቹን ሥራ
ያወራሉ።
ቀንም ለቀን
ታወጣለች ነገርን
ትናገራለች እውቀትን።
፪፡ እርሱ እንደ ሙሽራ
ከእልፍኙ ይወጣል፤
እንደ ኃያል በመንገዱ መሄድ
ደስ ይለዋል።
አወጣጡ
ከሰማይ ዳርቻ ነው
ዙረቱም እስከ ዳርቻው።
፫፡ የአምላክ ሕግ ፍጹም ነው
ነፍስን ይመልሳታል ሕፃናትንም
በሙሉ ጠቢባን ያደርጋል።
ያምላክ ሥርዓት
ቅን ልብን ደስ ያሰኛል
ትእዛዙ ዓይንን ያበራል።
፬፡ ያምላክ ፍርሃት ንጹሕ ነው
ለዘላለም ይኖራል
ፍርዱም እውነትና ቅንነት
በአንድነት ነው።
ከጠራ ወርቅ
ከዕንቍም ይወደዳል
ከማር ይልቅ ይጣፍጣል።
፭፡ የድፍረት ኃጢአት እንዳይገዛኝ
ባርያህን ጠብቅ፤
የዚያን ጊዜ ከታላቁ ኃጢአት
እነፃለሁ።
መድኃኒቴ፥
አቤቱ የአፌ ቃል
በፊትህ ያማረ ይሁን።