መዝሙር 220 ከሰማይ ማን ወረደ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ከሰማይ ማን ወረደ
ጌታ የሱስ ክርስቶስ።
ሕፃን ሆኖ ማን መጣ
ጌታ የሱስ ክርስቶስ።
ዘምሩ ለክብረቱ
አዳኛችን ነው እርሱ
መድኃኒትም ነው እርሱ
ጌታ የሱስ ክርስቶስ።
፪፡ ማን ሞተ በጎልጎታ
ጌታ የሱስ ክርስቶስ
ከሞት እኛን ሊፈታ
ሞተ የሱስ ክርስቶስ።
ዘምሩ . . .።
፫፡ ማነው ርኅሩህ ሁሉ ቀን
ጌታ የሱስ ክርስቶስ
ማን ይላል በእምነት ዳን
ጌታ የሱስ ክርስቶስ
ዘምሩ . . .።
፬፡ በሰማይ ያለው ማነው
ጌታ የሱስ ክርስቶስ
በእምነት የምናየው
ጌታ የሱስ ክርስቶስ
ዘምሩ . . .።
፭፡ ማን ይመለሳል ከላይ
ጌታ የሱስ ክርስቶስ።
ማን ያወርሰናል ሰማይ
ጌታ የሱስ ክርስቶስ።
ዘምሩ . . .።