መዝሙር 202 የሱስ ባርከህ ስጠኝ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ ባርከህ ስጠኝ የሕይወትን ሕብስት
ለደቀ መዛሙርትህ እንደ ሰጠህ።
ካድማሱ ባሻገር አንተን እንዳይህ
ነፍሴ ተጠምታለች ሕያው ቃልህን።
፪፡ ባርከህ እንደ ሰጠህ ያን ቅዱስ ሕብስት
በምሕረት ጐብኘኝ ጌታ ሆይ እኔን።
ሸክሜና ቀንበሬ ባንተ ይፈታል
ሰላሜም ፍጹም ይሆንልኛል።
፫፡ እንተ ነህ የሕይወት እንጀራ ለኔ
ቅዱስ ቃልህ ደግሞ መድኃኔቴ።
ከአንተ ጋር ልኑር ተመግቤ
እውነተኛ ፍቅርህን ቀምሼ።
፬፡ መንፈስህን አውርድ አሁን በኔ ላይ
ዓይኖቼንም ዳስስ አንተን እንዳይ።
እውነትህን ልመገብ ከቃልህ ውስጥ
ቅዱስ ፈቃድህን ለኔ ግለጥ።