መዝሙር 146 ኢየሱስ ይመጣል የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ኢየሱስ ይመጣል
በመላእክት ታጅቦ
በደሙ የዋጀውን
ለመውሰድ ሰብስቦ።
ያለ እንቅልፍ በትጋት
ነቅተው ለጠበቁት
ይመጣል ኢየሱስ
ዋጋቸውን ለመስጠት።
ትንቢት ተፈጸመ
መምጣቱ ነው ጌታ
ድልን እንድናገኝ
ሁላችን እንበርታ።
ትንቢት ተፈጸመ
መምጣቱ ነው ጌታ
ድልን እንድናገኝ
ሁላችን እንበርታ።
፪፡ እንደ ሄደ አይቀርም
ጌታችን ይመጣል
ዘመኑ አጭር ነው
ሁሉም ተፈጽሟል።
ጊዜው ሲፋጠን
እንዲህ እያየን
መንቃት ያስፈልጋል
ሲኦል እንዳይውጠን።
ትንቢት . . .።
፫፡ መምጣቴ ነው ብሎ
አዋጅ ያስነግራል
ይኸው የምሥራች
ዞትር ይሰበካል።
ድምፁን እየሰሙ
ለተከተሉት
ሲመጣ ይሰጣል
የዘላለም ሕይወት።
ትንቢት . . .።
፬፡ ጌታን አመስግኑ
በደሙ የነፃችሁ
መምጣቴ ነው ይላል
የሱስ ሊወስዳችሁ።
ስማችን የተፃፈ
በሕይወት መዝገብ
ጊዜው ተዳርሶአል
ልንሰበሰብ።
ትንቢት . . .።