መዝሙር 125 በአምላክ ተመርተን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በአምላክ ተመርተን በቃሉ ብርሃን
በልጁም ሲጸና የምሕረት ኪዳን
ያላየነው ዘመን ሲቀርብ አንፍራ።
ያ ቸር እረኛችን
ሲኖር በቅርባችን
ሲሄድ በፊታችን
ከምን እንፍራ?
፪፡ ከጨለማ ዓለም ከምድር ሥቃይ
አንድ ጭፍራ ተነሣ ሊጓዝ ወደ ላይ
የጭፍራው ገናንነት ተሰውሮአል።
ግን አምላክ ሲቀድም
ሲከተል ሲከብም
ሲደግፍ ሲሸክም
ይጋርደዋል።
፫፡ የዓለም ልጆች ከንቱነትዋን ሲሹ
በርኩሰትም ብቻ ሲሆን ደሰታቸው
ያን ጭፍራ ልከተል ሲሄድ ወደ ላይ
ያልታሰበውን ክብር
ያልታየውን ምሥጢር
የተስፋውን ነገር
ላገኝ በሰማይ።
፬፡ የደመና ዐምድ የእሳት ብርሃንም
ውኃ የሚሰጠው ሕያው ዓለትም።
ዘወትር ሊመሩን ይከተሉናል
ያንን ቅዱስ ዓለት
ብናምነው በእውነት
ለሞቱቱ ሕይወት
ሊሰጥ ይችላል።
፭፡ ያ ዓለትም ክርስቶስ አዳኛችን ነው
ያነጻንም ደም የፈሰሰው ውኃው።
የኃጢአታችን ሥርየት አለነ
በአንዱ በየሱስ
ያ ጻድቅ ያ ቅዱስ
ለምስኪን ለርኩስ
መድኃኒት ሆነ።
፮፡ በሰይጣን ስጨነቅ ተስፋ ስቆርጥም
መድኃኒቴ ሆነ የልቤ ሰላም
በመስቀሉ ሞተ ለሁሉ ኃጥአን።
ለሁሉ ከሞተ
ሁላችን ሞትን
ለሁሉም ከሞተ
ተገኘ መዳን።
፯፡ በአምላኬ ፊት በደለኛ ስሆን
በየሱስ ሳምን ማን ይከሰኝ ይሆን?
በየሱስ በልጁ የጸደቅሁ ነኝ።
በእርሱም ሲያየኝ
አንድ ርኩሰትም የለኝ።
ያምላክ ስምረት አለኝ
በየሱስ ስገኝ።
፰፡ ቃሉም የብፅዕና መያዣዬ ነው
የየሱስ ሥቃይ መጽናናቴ ነው
በሞቱ በትንሣኤው አድኖኛል።
መድኃኒቴ ሳለ
ረድኤቴ ዘወትር አለ።
መድኃኒቴ ሳለ
በተስፋ ልኑር።
፱፡ ኦ የሱስ ያልተውኸን እስከ አሁን
መታመንህ ብቻ ተስፋችን ይሁን
ተሸከመን ጋርደን ከእኛም ዘንድ ሁን።
አሜን ለዘላለም
ምስጋና ስብሐት
ለአምላክ ለበጉም
ዘወትር ይሁን።