Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 12 ማርያምም እንዲህ አለች በምስጋናዋ የዘፈን ግጥሞች

መዝሙር 12 ማርያምም እንዲህ አለች በምስጋናዋ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009

 

፩፡ ማርያምም እንዲህ አለች በምስጋናዋ
ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች
መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ
በማዳኑ ተስፋ ሐሴት ታደርጋለች፡፡
የባርያይቱን መዋረድ አይቶአልና
ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፡፡
፪፡ ብርቱ የሆነ እርሱ በኔ ታላቅ ሥራ
አድርጎአልና ታላቅ ነው ቅዱስ ነው፡፡
ለሚፈሩት ምሕረቱ ለልጅ ልጅ ይኖራል
በክንዱ ታላቅ ኃይል አድርጎአልና፡፡
ምሕረቱን ለዘለዓለም እያሰበ፡፡
እንደተስፋው ብላቴናውን ረድቶአል፡፡
፫፡ በፊቱ ዝቅ ዝቅ እንበል በትሕትና
በቤቱ እንኑር ዘወትር በምስጋና፡፡
በአምላክ ግርማ ፊት እንዘምር በፍሰሐ
እነሆ ባሮችህ ፈቃድህ ይሁን እንበል
የሚያበራ ቃል ከኛ ጋር ይኖራል
ጸጋና እውነት አልፋና ዖሜጋ። አሜን፡፡

Exit mobile version