መዝሙር 12 ማርያምም እንዲህ አለች በምስጋናዋ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ማርያምም እንዲህ አለች በምስጋናዋ
ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች
መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ
በማዳኑ ተስፋ ሐሴት ታደርጋለች፡፡
የባርያይቱን መዋረድ አይቶአልና
ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፡፡
፪፡ ብርቱ የሆነ እርሱ በኔ ታላቅ ሥራ
አድርጎአልና ታላቅ ነው ቅዱስ ነው፡፡
ለሚፈሩት ምሕረቱ ለልጅ ልጅ ይኖራል
በክንዱ ታላቅ ኃይል አድርጎአልና፡፡
ምሕረቱን ለዘለዓለም እያሰበ፡፡
እንደተስፋው ብላቴናውን ረድቶአል፡፡
፫፡ በፊቱ ዝቅ ዝቅ እንበል በትሕትና
በቤቱ እንኑር ዘወትር በምስጋና፡፡
በአምላክ ግርማ ፊት እንዘምር በፍሰሐ
እነሆ ባሮችህ ፈቃድህ ይሁን እንበል
የሚያበራ ቃል ከኛ ጋር ይኖራል
ጸጋና እውነት አልፋና ዖሜጋ። አሜን፡፡
