መዝሙር 114 ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ
ቅዱስ የአምላክ በግ።
ክቡር ክቡር ክቡር
ክቡር የአምላክ በግ።
ስብሐት በሰማይ ለምትኖር
ንጉሥ ነህ በሰማይ በምድር።
ስብሐት በሰማይ ለምትኖር
ቅዱስ የአምላክ በግ።
፪፡ ቅዱሰ ቅዱስ ቅዱስ
ልዑል ጌታችን።
ይንገሥ ይንገሥ ይንገሥ
መድኃኒታችን።
ፍጥረት ሁሉ ይስገዱለት
ግሩም ሥራው ይደነቅለት።
ሃሌ ሉያ ኑ ዘምሩለት
ቅዱስ ያምላክ በግ።