መዝሙር 109 ሃሌ ሉያ አምላካችን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ሃሌ ሉያ አምላካችን፥
በመቅደሱ ይመስገን።
እናመስግነው ሁላችን፥
በኅብረት ተሰብስበን።
ሃሌ ሉያ እናመስግን፥
በችሎታው ይመንስገን።
ታላቅነቱን እያሰብን፥
እንወድሰው አሁን።
ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ ሉያ፥
ሕይወት ያለው ያመስግን፤
በመልካም ድምፅም ያመስግን፤
ያቅርብለትም ውዳሴን፤
በመልካም ድምፅም ያመስግን፤
ያቅርብለትም ውዳሴን።
፪፡ ኑ አምላክን እናመስግን፥
በከበሮና ዜማ።
እንደ ታላቅነቱ መጠን፥
በእንቢልታ ይመስገን።
ሃሌ ሉያ እናመስግን፥
በመሰንቆ አድርገን።
እናመስግን ጌታችንን፥
እናክብርው አምላክን።
ሃሌ ሉያ፥ . . .።