Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 53 በቀረበ ጊዜ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ በቀረበ ጊዜ
የፋሲካ በዓል፥
እንዲህ ብለው አሉት
ተማሮቹ ባንድ ቃል።
፪፡ አቤቱ መምህር ሆይ
ከአብ ዘንድ የመጣህ፥
ፋሲካን በወዴት
እናዘጋጅልህ?
፫፡ ይህንን ስላሉት
ጌታም አዘዛቸው፥
ሂዱ በፊታችሁ
ታገናላችሁ ሰው።
፬፡ ውኃ ተሸክሞ
ሲሄድ ወደ ጌታው፥
እንዲህ ብላችሁ
ጠይቁት ያንን ሰው።
፭፡ እባክህ አሳየን
የማረፊያ ስፍራ፥
መምህር የሚያርፍበት
ከተማሮች ጋር።
፮፡ ያሳያችሁማል
ጥሩውን እልፍኝ፥
ፋሲካን ለመብላት
በዚያ አዘጋጁልኝ።