Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 333 ኢየሱስ ክርስቶስ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወዳለም መጥቶአል
ኃጢአተኞችን ለማዳን፤
እርሱንም ማመንና መቀበል
ሕይወትና ጽድቅ ይሆነናል።
፪፡ በመላ ዓለም ወንጌል ይሰማል፤
ማዳኑ በዚህ ይገለጣል፤
ቅዱስ ቃሉን ሰምተው ሲቀበሉ
አሕዛብ በምነት ይድናሉ።
፫፡ በየሱስ ኃይል ዕውራን ያያሉ
የዲዳ አፍም ይናገራል፤
ሽባዎች፤ አንካሶች ይድናሉ፤
ሙታንም ደግሞ ይነሣሉ።
፬፡ በዚህ የወደቀውን ደረቅ አጥንት
ጌታ ኢየሱስ ሆይ ተመልከተው፤
አሁን ሥጋና ጅማት አልብሰህ፥
የሕይወትን እስትንፋስ ስጠው።
፭፡ አሕዛብ በእግርህ ታች ይስገዱ
ለክብርህ ያቅርቡ ምስጋና።
ከጸጋ ምንጭ ሕይወትን ይውሰዱ፤
ስምህ ይቀደስ ሃሌ ሉያ።