Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 325 ለዚህ ዓለም ባዕድ ሆነን የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ለዚህ ዓለም ባዕድ ሆነን
የሱስን እንጠብቃለን።
እዚህ ነዋሪ ቤት የለንም
ርስታችን በሰማይ ቤት ነው።
ቤታችን ፈራሽ ድንኳን ነው
እስክንሄድ ከዚህ ዓለም
የሱስ ይመጣል ከሰማይ
ሊያወርሰን ርስታችንን።
፪፡ በመከራ በስደትም
አንመረር አናጕረምረም፤
ላጭር ጊዜ እንቆያለን
የሱስ መጥቶ እስኪወስደን።
ቤታችን . . .።
፫፡ ባዲሲቷ የሩሳሌም
እንግዶች በማንሆንበት፥
ከጌታ ጋር ባለ እርስቶች
እንሆናለን ያምላክ ልጆች።
ቤታችን . . .።
፬፡ የግብፆችን አገር ለቀው
እንደወጡ ስደተኞች፥
እንገስግስ እኛም ወደፊት
ወደ ሰማይ የተስፋ ርስት።
ቤታችን . . .።