Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 32 የሱስ ሆይ፥ ያንተ ሕማማት የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የሱስ ሆይ፥ ያንተ ሕማማት
ያንተ ቁስልና ሞት
ይሰጠኛል መጽናናት።
በሚደርስብኝ ጭንቀት
ሥጋዬን ሲፈትነኝ
ሕማምህን አሳስበኝ።
ቅዱስ ጌታ ሆይ ጠብቀኝ
በጸጋህም ድልን ስጠኝ።
፪፡ ክፉ ሥጋ ወደ ፍትወት
ሲያዘነብል ለውድቀት
ቁስልህን ስመለከት
እድናለሁ ከጥፋት
ሰይጣንም ሲፈትነኝ
በጸጋህ ኃይልህን ስጠኝ
እርሱ ግርማህን ይፈራል
ከፊቴም ቶሎ ይሸሻል።
፫፡ የሱስ ሆይ የነፍሴ ጌታ
አንተ የኔ አለኝታ።
ምንም ጭንቀት ቢበዛብኝ
በልቤ ሰላም አለኝ።
እንተ ስለ ዋጀኸኝ
ለዘላለም ሕያው ነኝ።
በምሕረትህ ጠርተኸኛል
ጽድቅን አጎናጽፈኸኛል።
