Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 317 አዲሲቱ ኢየሩሳሌም የዘፈን ግጥሞች
፩፡ አዲሲቱ የሩሳሌም
ተሠርታለች በላይ፤
በዚያ ሰላምና ደስታ
ስጠኝ አምላኬ ሆይ።
በዚህ በምድር ግን ፍርሃት
ሁከትም በዝቶአል፤
ቢቀልም እንኳ መከራ
ድካምም ሞልቶአል።
፪፡ እንዲህ ከሆነ ሁልጊዜ፥
ወደ ኢየሩሳሌም
ብናፍቅ አያስደንቅም።
ብመኝ አይገርመኝም
ቤቴ እና ዝምድናዬ
ትውልዴም ከዚያ ነው
ግን በዚህ በእግንድነቴ
ነፃነት የለኝም።
፫፡ በእውነት የቸር አምላክ ልጅ
ልሆን ተወለድሁኝ፤
ከሰይጣን ኃይል ከሕግም ፍርድ
አርነት ወጣሁ።
በየሱስ ክርስቶስ ለነፍሴ
መዳን ካገኘሁ፥
የአምላክ ልጅ በጸጋው ነኝ
ባሪያ አይደለሁም።
፬፡ ሊያድነኝ በመስቀል ላይ
በሞተው አምኜ፥
በሰጠኝ ጸጋ ውስጥ ልኑር።
እርሱን ተማጥኜ።
በአብ ዘንድ አማላጅ ሆኖ
ከቆመ ስለኔ፥
በርሱ ሲያየኝ ጸድቅ ነኝ
በርሱ በመድኀኔ።
፭፡ ግን በምድር በሕግ ሥራም
ሊድን ለሞከረ፥
ስለርሱ መድኀኑ ሲሞት
በከንቱ ነበረ።
በእምነት ጻድቅ እንዲድን
ነብዩ ነገረ፥
በክርስቶስ ሞት ሙሉ መዳን
ለእኛ ተገኘ።
፮፡ ስለኔ ነፍሱን ለውጦ
ፍጹም በወደደኝ፥
በኔ ሳይሆን ግን በክርስቶስ
በእምነት ሕያው ነኝ።
ከእርሱ ጋር ተሰቅዬ
መናኝ በዓለም ነኝ፤
የዓለም ወዳጅ ለመሆን
ምን ምክንያት አለኝ።
፯፡ ወዳምላክ ከተማ ስደርስ
ከምድሩ ሥቃይ፥
ዕረፍት ሰላምም ደስታም
ይሰጠኛል በላይ።
ልቅሶ፥ ማጣጣር ጩኸትም
አይገኝም በሰማይ፥
ሌትም አይሆንም ያምላክ በግ
ነው ያገሩ ፀሐይ።
፰፡ በእንጨት የተሰቀለውን
መድኃኒት ካመንሁ፥
በምድር የሚወደደውን
መሻት ትቻለሁ።
አንድ ነገር ብቻ ፈልጌ
እርሱን ተመኘሁ፥
ወዳንቺ ኢየሩሳሌም
ለመድረስ ናፈቅሁ።