Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 315 አንድ ቀን የዘፈን ግጥሞች
፩፡ አንድ ቀን፥ በቅዱስ አምላክ ፊት፥
ከሰው ነገዶች ሁሉ፥
ሊቆጠሩ የማይችሉ
ጸድቃን ይቆማሉ።
፪፡ አንድ ቀን፥ ያምላክ አገልጋዮች፥
በመከሩ ወራት፥
ያያሉ ከተማሩቱ
የእለፍ አእላፋት።
፫፡ ሊሰጠን በሰማይ ጸዳል
ሰላምም ብፅዕናም፤
ምንኛ ደስታ ይሆናል፥
ምንኛ ምስጋናም።
፬፡ አምላክ ሆይ፥ ጸጋህ ብዙ ነው፤
ወዳንተ አቅርበን፤
ከጻድቃን ጋር እንድንገኝ
በዚያ ታላቅ ቀን።