Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 298 ሳዝን ስንገላታ የዘፈን ግጥሞች
፪፡ ሳዝን ስንገላታ
ጠላቴም ሲያጠቃኝ፥
ፈተና ሲከበኝ
ቀን ሲጨልምብኝ
የሱስ አንተ ብቻ ነህ
ልትረዳኝ የምትችል፥
እምነቴ ባንተ ነው
ሌላ አምባ የለኝም።
እረኛዬ፥ እረኛዬ፥
እረኛዬ ከለላዬ፤
አንተ እኮ ነህ አለኝታ ጠባቂዬ፤
ኢየሱሴ፥ ኢየሱሴ
ኢየሱሴ መከታዬ፤
አንተ እኮ ነህ አለኝታ ጠባቂዬ።
፪፡ ስማኝ ጌታ የሱስ፥
ችግሬን ተመልከት፤
ልቤን አሳርፈው
ከኀዘን ከጭንቀት።
የእኔን ኀዘን አይተህ
ልብህ የሚራራ፥
ጌታ ሆይ አንተ ነህ
የእኔ ጽኑ ተስፋ።
እረኛዬ . . . .።
፫፡ በስደት፥ በችግር፥
በሚያስፈራው ሞገድ፥
በዓለም ጉዞዬ
በጨለማ መንገድ፥
ደግፈኝ ኢየሱስ
ከኔ ጋር ተራመድ፤
አላፊውን ደስታ
ልቦናዬ እንዳይወድ።
እረኛዬ . . .።
፬፡ ሥጋ ደካማ ነው፤
ሁሉንም ይመኛል፤
ስሜትም ክፉ ነው፤
ከውድቀት ያደርሳል።
ከዚህ ሁሉ ውድቀት
ጠብቀኝ ጌታዬ፥
እምነቴን አጽናልኝ
ሁነኝም መሪዬ።
እረኛዬ . . .።