Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 272 ጌታን ስንከተል የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ጌታን ስንከተል
በቃሉ ብርሃን፥
ብፅዕናን ክብርን ይሰጠናል።
በየሱስ ብናምን፥
በኛ ውስጥ ይኖራል።
እንታዘዘው እናክብረውም፥
እንመነው እንገዛለትም፥
ሌላ መንገድ አይገኝም፥
የሚሰጥ ሰላምን።
፪፡ ችግር ቢበዛብን፥
ፍርሃትም ቢይዘን፥
ፍቅሩ ነው ሁሉን የሚገዛ።
ለሥቃይና ሞት
ራሱን ሰጠ ቤዛ፤
ስለዚህ ለርሱ እንገዛ።
እንመነው . . .።
፫፡ ሁሉን ብንታገሥ፥
ብንችል መከራን፥
በየሱስ እናሸንፋለን።
ታግሶ እስከ ሞት
አጠፋው ኃጢአትን፥
ስለዚህ እንጽና በእምነት።
እንመነው . . .።
፬፡ በፍቅሩ ደስታን
ይወዳል ሊሰጠን፥
ለእርሱ እንስጥ ልባችንን።
ምሕረትን ደስታንም
ጸጋንና ፍቅርን
ከቶ ለማይወዱት አይሰጥም።
እንመነው . . .።
፭፡ ነጽተን ከኃጢአት
በቅዱስ አንድነት
እንኖራለን በሰማይ ቤት።
አምላክን አክብረን
ስንኖር በዕረፍት
እናቀርባለንም ምስጋና።
እንመነው . . .።